tg-me.com/mnenteyiklo/2821
Last Update:
ጥያቄ :- ሰላም እንዴት ናችሁ?
ጥያቄ ለመጠየቅ ነበር መናፍቃን እኛ ኦርቶዶክሳውያንን አንዲት ጥምቀት ተብሎ ተጽፎ ለምን በየዓመቱ ትጠመቃላችሁ? ብለው ይጠይቃሉ ቢያብራሩልን።
መልስ
👉 ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሚለው መጽሐፋቸው የዚህን ጥያቄ መነሻና ምላሹን እንዲህ ብለው ጽፈዋል። "የጠበሉን መረጨት አይተው በቀድሞ ዘመን ወደ ሀገራችን መጥተው የነበሩ ኢየሱሳውያን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ታጠምቃለች ብለው ጽፈዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ይህን የምትፈጽመው ጌታችን ለእኛ ብሎ ያሳየውን ትህትና ለመመስከር ለምዕመናን በረከተ ጥምቀትን ለማሳተፍ እንጂ የተጠመቁትን ምዕመናን እየመላለሰች በየዓመቱ አታጠምቅም። ጥምቀት አሐቲ [አንዲት] መሆኗን ታውቃለችና። [የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ.126]
ዲያቆን ብርሃኑ አድማስም በዓላት በሚለው መጽሐፉ በጥምቀት የምንጠመቀው ለሥርየተ ኃጢአት ጭምር መሆኑን ሲገልጽ እንዲህ ብሎአል። "የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያንም ለዚሁ አንጽሖተ ማይ (ውሃውን ለመቀደስ) እና ምእመናኑም በጥምቀት (በልጅነት) የቀደመ ኃጢአታቸው የተሠረየላቸውን ያህል በዚህ ዕለትም የሠሩት ኃጢአት ይሠረይላቸዋል ትላለች። [በዓላት፤ ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ገጽ ገጽ.71] ስለዚህም በረከተ ጥምቀቱን ለምዕመናን በማድረስ ማሳተፍና ሥርየተ ኃጢአትን መስጠት እንጂ መላልሶ ማጥመቅ አይደለም። ልጅነት አንድ ጊዜ ብቻ ነውና።
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት። ኤፌ.{ 4:5። ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት አትደገምም። በጸሎተ ሐይማኖት ላይም "ኃጢአት በሚሰረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን" ይላል። ጥምቀት ከምናከብራቸው ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ጌታችን በቅዱስ ዮሐንስ ሊጠመቅ መሄዱን የምናስብበት በዓል ነው ከጌታችን ጥምቀትም በረከትን የምንሳተፍበት በዓል ነው። ጥምቀት ሊደገም ይቅርና ይህን የጌታን ጥምቀትን በማሰብ የምናከብረውን በዓል ለማክበር መብቱ እንኳ ያላቸው ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ በጥምቀት የሥላሴ ልጅነትን ያገኙ ክርስቲያኖች ናቸው። ስለዚህ በረከተ ጥምቀትን ለመሳተፍ እንጂ ልጅነት የምታሰጠዋ ጥምቀት የምትደገም ሆና አይደለም።
ጌታችን በወንጌል " የክርስቶስ ስለ ሆናችሁ በስሜ ጽዋ ውኃ የሚያጠጣችሁ ሁሉ፥ ዋጋው እንዳይጠፋበት እውነት እላችኋለሁ።" ማር.9:41 እንደተናገረ ስሙን አስበን የምናደርጋቸው የምንዘክራቸው የጌታን ዓበይትና ንዑሳን በዓላትን ማሰብ መዘከር ስለ እርሱም ብሎ ነዳያንን በምሕረት መጎብኘት ዋጋ የማያሳጣ ተግባር ነው።
✍ ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]
BY ምን እንጠይቅሎ?
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2821